የሰላምና አንድነት ማህበር የዋሺንግተን ዲሲ ግብረ ሃይል ተወካዮች በወቅታዊ የአገራችን ጉዳዮች ዙሪያ በኤምባሲያችን በመገኘት ውይይት አድርገዋል።

በግብረ ኃይሉ እና አጠቃላይ በዳያስፖራው ማህበረሰብ የሚነሱ ከሰላምና ጸጥታ፣ ከህገ-መንግስት እና ሌሎች ጉዳዮችን አስመልክቶ ጥያቄያቸውን በደብዳቤ ለክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለ ሰጥተዋል።

አምባሳደር ስለሺ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በአገራቸን ለውጥ እንዲመጣ ብሎም ሲደረጉብን የነበሩ ኢ-ፍትሃዊና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተጽእኖዎች በመቃዎም ግብረ ኃይሉ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።
በቃል እና በደብዳቤ የቀረቡ ጥያቄዎችን ለሚመለከተው የመንግስት አካል እንዲደርስ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል።

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *