በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ…
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው የሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች ዛሬ በኤምባሲያችን ተገኝተው ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል። ክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለም የሰልፉ አስተባባሪዎችንና የእምነቱ ተወካይ አባቶችን አነጋግረዋል። በተወካዮቹ በኩል የቀረቡ ጥያቄዎችን ተቀብለው ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እንደሚያደርሱም ቃል ገብተዋል።
