ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ
ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአሜሪካን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ገለጻ ለመስጠት እ.ኤ.አ. ሜይ 8 ቀን 2025 በጠሩት መድረክ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል። በወቅቱም ክቡር አምባሳደሩ ከአሜሪካን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳኡ ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየታየ ላለው አጠቃላይ ለውጥ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ክቡር አምባሳደሩ በበኩላቸው የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ያለበትን ሁኔታ አስመልክቶ ከምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጋር የተለዋወጧቸው ሀሳቦች በቀጣይ በተደራጀ መልኩ ለሚደረጉ መስተጋብሮች አጋዥ እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

H.E. Ambassador Binalf Andualem took part in an event organized by U.S. Secretary of State Marco Rubio for a briefing on the current State of the Administration on May 8, 2025. During the event, Ambassador Binalef met with Christopher Landau, the Deputy Secretary of State of the U.S., and they exchanged ideas. The Deputy Secretary acknowledged the overall improvements in Ethiopia and expressed commitment to working together. Ambassador Binalf conveyed his confidence that their discussion on the state of the relationship between Ethiopia and the United States will serve as a foundation for future structured engagements
Leave a Reply
Want to join the discussion?Feel free to contribute!