6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ዕጩዎች ያቀረቡ ፓርቲዎች ዝርዝር ይፋ ተደረገ (March 12, 2021)

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ዕጩዎች ያቀረቡ ፓርቲዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

በዝርዝሩ መሰረት 125 እጩዎች በግል የሚወዳደሩ፣ አራት ፓርቲዎች ለክልል ምክር ቤት ብቻ የሚወዳደሩ ሲሆኑ ሁለት ፓርቲዎች ደግሞ ለተወካዮች ምክር ቤት ብቻ የሚወዳደሩ ናቸው።

ዕጩዎች ያቀረቡ ፓርቲዎች ዝርዝር

1. ሐረሪ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

2. ሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

3. ራያ ራዩማ ዴሞክራቲክ ፓርቲ

4. ቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

5. ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ

6. ብልፅግና ፓርቲ

7. ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

8. ኅዳሴ ፓርቲ

9. ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ

10. አዲስ ትውልድ ፓርቲ

11. እናት ፓርቲ

12. ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ

13. የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

14. የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ

15. የጋሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

16. የጌድዮ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

17. የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት

18. የሲዳማ ሕዝብ አንድነት ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

19. የሲዳማ አንድነት ፓርቲ

20. የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

21. የቤንሻንጉል ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ

22. የአገው ብሔራዊ ሸንጎ

23. የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ

24. የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ

25. የአርጎባ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት

26. የአርጐባ ብሔረሰብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ

27. የአፋር ሕዝብ ፓርቲ

28. የአፋር ነፃ አውጪ ግንባር ፓርቲ

29. የአፋር አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር

30. የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ

31. የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ

32. የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ

33. የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ

34. የኢትዮጵያ ነፃነት ፓርቲ

35. የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ-ፍትህ ፓርቲ

36. የኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ኅብረት

37. የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር

38. የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ

39. የካፋ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት

40. የወለኔ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

41. የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር

42. የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ

43. የዶንጋ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት

44. የጋምቤላ ህዝቦች ፍትህ ለሰላም እና ልማት ዴሞክራቲክ ንቅናቄ

45. የምእራብ ሶማሌ ዴሞክራቲክ ፓርቲ

46. የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ

47. የካፋ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ህብረት

No photo description available.
0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *