Entries by Embassy Content Editor

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት ይደግፋል − በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የአሜሪካ መንግስት እንደሚደግፍ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አስታወቁ፡፡ ኢትዮጵያ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያስመዘገበች መሆኗንም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል። በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንደምትሰራም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እንደምትሰራ በአጽንኦት መግለጻቸው ይታወሳል። ኢትዮጵያ […]

ክቡር አምባሳደር በስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ረዳት ፀሃፊ ጋር ተወያዩ

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም በስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ረዳት ፀሃፊ ቪንሴንት ዲ. ስፔራ ጋር በኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገናኝተው በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እየተደረገ ያለውን ጥረት ጨምሮ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ የተለዋወጡ ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ምክትል ረዳት ፀሃፊው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢኮኖሚያዊ ትብብር የሚሰጠውን ትኩረት አፅንዖት […]

SelectUSA Investmenet Summit-2025 ላይ ለመሳተፍ ከኢትዮጵያ የመጡ ባለሀብቶች ጋር ውይይት ተካሄደ፤

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም SelectUSA Investmenet Summit-2025 ላይ ለመሳተፍ ከኢትዮጵያ የመጡ ባለሀብቶች ጋር በኤምበሲያችን ውይይት ያካሂዱ ሲሆን በመድረኩ የኢትዮ-አሜሪካ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ ፕሬዝዳንትና ቦርድ አባላት፣ የአሜሪካ ኮሜርስ ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ተጠባባቂ ዳይሬክተር እንዲሁም በአሜሪካ የዲ.ኤም.ቪና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን ባለሀብቶች እና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች፣ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላለፍዋል፡፡ […]

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ጋር ተወያዩ፤

ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ዋሽንግተን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ጋር በሚሲዮኑ በመገኘት ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በሚሲዮኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊተገበሩ በሚገባቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ካነሷቸው ነጥቦች መሃከል ዲፕሎማቱና መላው ሰራተኛ በፖለቲካ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ፣ ሃብት ማፍራት፣ ወጪ ቅነሳ እንዲሁም ዲያስፖራ ጉዳዮችና ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በቡድን መንፈስ […]

የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢቨንትስ ዲሲ ጋር ውይይት አደረገ

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ ታላላቅ ስብሰባዎችን፣ መዝናኛዎችን፣ ስፖርታዊ እና ባህላዊ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ኢቨንትስ ዲሲ ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስ ጌትስ እና ሎሎች አመራር አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል። ክቡር አምባሳደሩ ባደረጉት ንግግር የአዲስ አበባ እና የዋሽንግተን ዲሲ ከተሞች ያላቸው እህትማማች ግንኙነት ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከማጠናከር […]

ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን አስመልክቶ የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ።

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ በተለያዩ ስቴቶች ከሚኖሩ የዳያስፖራ አደረጃጀት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና በውሃ ዙሪያ የሚሰሩ ተቋማት አደረጃጀቶች አመራርና አባላት ጋር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የህዳሴ ግድብ በተለያየ ፈተና ውስጥ አልፎ ዛሬ እዚህ በመድረሱ እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ይህ […]

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአሜሪካን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ገለጻ ለመስጠት እ.ኤ.አ. ሜይ 8 ቀን 2025 በጠሩት መድረክ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል። በወቅቱም ክቡር አምባሳደሩ ከአሜሪካን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳኡ ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየታየ ላለው አጠቃላይ ለውጥ እውቅና የሰጡ […]

የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በሜኔሶታ ከክልሉ ተወላጆች ጋር ውይይት አደረጉ

እ.ኤ.አ. ሜይ 3 ቀን 2025 የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በአሜሪካ ሜኔሶታ ግዛት ነዋሪ ከሆኑ የክልሉ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ጋር በክልሉ እየተካሄደ ባለው የልማት ስራዎች እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረጉ። ርዕሰ መስተዳድሯ በክልሉ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ እና እየተካሄደ ስላለው የልማት እንቅስቃሴ እንዲሁም ከዳያስፖራው ምን እንደሚጠበቅ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በክልሉ ያለው […]

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ። ክቡር አምባሳደሩ ከሴናተሩ ጋር ሲገናኙ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን በዚህ ውይይታቸውም በአፍሪካ ንኡስ ኮሚቴ ሥራ እንዲሁም ንኡስ ኮሚቴው አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ከማሳደግ አንጻር ባለው ሚና ላይ ተወያይተዋል። ሁለቱም ወገኖች በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢትዮጵያ መካከል […]

“ሠላም ፍትህና ዕድገት ለኢትዮጵያ” ከተሰኘ የዳያስፖራ ምሁራን ህብረት ጋር ውይይት ተካሄደ

“ሰላም፣ ፍትህ እና ዕድገት ለኢትዮጵያ” የተሰኘ የዳያስፖራ ምሁራን ህብረት አባላት የካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ከክቡር አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በበይነ-መረብ መድረክ ውይይት አደረጉ።በውይይቱ ወቅት የህብረቱ አባላት በትኩረት ካነሱዋቸው ጉዳዮች መካከል በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵየዊያን ለሀገራቸው በእውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና አቅማቸው በሚፈቅደው ሁሉ ለአገራቸው ሰላምና እድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባቸው፣ […]