Embassy hosted a reception for the diplomatic community…

On July 3, 2025, the Embassy hosted a reception for the diplomatic community in Washington, D.C. Ambassadors and members of the diplomatic corps attended the event, which had a remarkable level of representation and turnout.

This gathering offered a great opportunity to engage with the diplomatic community and set the stage for future collaborations.

Guests also enjoyed a selection of Ethiopian delicacies and, of course, Ethiopia’s renowned coffee.

በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኙ አምባሳደሮች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት የተገኙበት ፕሮግራም ተካሄደ።

በአሜሪካን ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከተለያዩ አገራት የተወከሉ ዲፕሎማቶችን ያስተናገደ ዝግጅት ያካሄደ ሲሆን ፕሮግራሙ በዲፕሎማቶች መካከል የትውውቅ፣ ትብብር እና ትስስር ለማድረግ በር የከፈተ መሆን ችሏል።

ታዳሚዎችም በኢትዮጵያዊ ምግቦች እና በተወዳጁ የኢትዮጵያ የቡና ጣዕም ተደስተዋል።

በዲ.ኤም.ቪና አካባቢዉ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማሰሪያ የመጨረሻ ዙር የነፃ ልገሳ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸዉ ተገለጸ፤

እ.ኤ.አ ጁን 19/2025 በዲ.ኤም.ቪ እና አካባቢዉ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በተገኙበት ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ገቢ ማሰባሰቢያ የእራት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡

በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ሁነት ላይ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሜሪላንድና በቨርጂኒያ (DMV) የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የግል ባላሃብቶች፣ አደረጃጀቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት አመራሮች፣ ታዋቂና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በተለይ ደግሞ ከዚህ ቀደም ለግድቡ ግንባታ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያከናውኑ የቆዩ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የነቃ ተሳትፎ የታየበት ሲሆን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የህዳሴ ግድብ መላው ኢትዮጵያውያንን በአንድንት ያስተሳሰረ የኩራታችን መገለጫ ነዉ ብለዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ ከበርካታ ዉጣ ዉረዶች በኋላ መንግስት በወሰዳቸዉ ቆራጥ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች በተገኘ ዉጤት በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የመጨረሻ ምዕራፍ ዋዜማ ላይ በመናኘታችን እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጨረሻ ምዕራፍ ከ 2 ፐርሰንት ያነሰ ስራዎች ብቻ የቀሩት መሆኑንና ይህንንም ለማጠናቀቅ እንዲቻል እንደ ከዚህ ቀደሙ አሻራችንን ለማስቀመጥ ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፤ ዲያስፖራው ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በመቀጠልም ዳያስፖራዉ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ ላበረከተዉ የበኩሉን ድርሻ እና እስካሁን ላደረገዉ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ የዕዉቅና እና የምስጋና ሰርተፊኬት በኤምባሲዉ ተበርክቶላቸዋል፡፡

በዕለቱም ለግድቡ ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ዙር ገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ አንድ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ (122,000) የአሜሪካ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም ሰላሳ አራት ሺህ ስምንት መቶ ሁለት (34,802.00) የአሜሪካን ዶላር ቦንድ ከሃገር ቤት ለመግዛት ቃል የተገባ ሲሆን በዚህ ዓመት እስከ አሁን ድረስ ከዩናትድ ስቴትስ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በድምሩ ሁለት መቶ ሰላሳ አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ አራት (231,174) የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በዚህ ፕሮግራም ላይ አንድ ሀገር ወዳድ ታዋቂ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የግል ባለሃብት ከ2021-2024 ባሉት ጊዜያት ዉስጥ ብቻ ከአንድ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጄክት ማሰሪያ የነጻ የገንዘብ ድጋፍ ማበርከታቸዉ ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑ ተነስቶ ለዚህም ታላቅ ምስጋና እና ዕዉቅና ተሰጥቷል።

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተመንግስት ተገናኝተዋል።

በአሜሪካ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ከፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ ጋር በነጩ ቤተመንግስት የመጀመሪያ ግንኙነታቸዉን አካሂደዋል። አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ነጩ ቤተመንግስት ሲደርሱ በኢትዮጵያና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ ግንኙነት የሚያንጸባርቅ ዲፕሎማሲያዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ይኸው ግንኙነት በቀጣይ ጊዜአት ለሚደረጉ በርካታ ውይይቶች መጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ጠንካራ ግንኙነት ያላቸው ሲሆን በሁለቱ አገራት መካከል እንደ ሰላም፣ ጸጥታና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ አጋርነት ከመፍጠር አንጻር ያሉ ዕድሎችም ሰፊ ናቸው። አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በውይይቱ ወቅት የተገኙትን ስቴት ሴክሬተሪ ማርኮ ሩቢዮ ጋርም ተገናኝተዋል።

H.E. Binalf Andualem, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of Ethiopia to the United States, held his first meeting with President Donald J. Trump at the White House. He received a formal diplomatic welcome, which reflects the longstanding relationship between Ethiopia and the United States. This meeting marks the beginning of many future discussions. The potential for a strong partnership in areas such as peace, security, and economic cooperation between the two countries is limitless. Ethiopia and the United States have enjoyed a robust relationship that spans over 120 years. During this occasion, the Ambassador also had the opportunity to meet with Secretary of State Marco Rubio.

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም አምባሳደር ቲቦር ናጊን በኤምባሲው ተቀብለው አነጋገሩ፤

በውይይታቸው የኢትዮጵያና አሜሪካን ግንኙነት ያለበትን ደረጃ የፈተሸ ጥልቅ ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር የሚያግዙ መልካም ሀሳቦችን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ እያካሄደች ያለችው የሃገር-በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳዳር ለኢኮኖሚ ግንኙነት ከሰጠው ከፍተኛ ትኩረት ጋር መገጣጠም ለሁለቱ አገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት የፈጠራቸው ልዩ እድሎችን አሟጦ መጠቀም በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል።

በተጨማሪም የሁለቱ አገራትን ሀብት ውጤታማ በሆነ መንገድ በማስተባበር በአካባቢው ሰላምና ብልጽግና ሊረጋገጥ በሚችሉባቸው መንገዶች ዙሪያ ሀሳቦችን የተለዋወጡ ሲሆን ለኢትዮጵያ ሰላምና ብልጽግና ከሚመኝ እውነተኛ ወዳጅ ጋር የሚደረግ እንዲህ አይነት ውይይት ጠቀሜታው እጅግ ከፍ ያለ መሆኑን ክቡር አምባሳደር ብናልፍ ገልጸዋል፡፡ ሁለቱም ወገን ለነበራቸው ፍሬያማ ውይይት ምስጋና አቅርበዋል።

H.E Ambassador Binalf Andualem welcomed Ambassador Tibor Nagy at the embassy for an in-depth discussion about the current state of relations between Ethiopia and the United States.

The conversation was insightful and rich, contributing to ongoing efforts to strengthen this historic partnership. They evaluated how to maximize the unique opportunities presented by the Home-grown Economic Reforms in Ethiopia, coupled with the Trump Administration’s focus on enhancing economic relationships, to accelerate trade and investment between the two countries. Additionally, they exchanged views on regional peace and security, sharing ideas on how to best collaborate and leverage the resources of both countries to promote peace and prosperity. Ambassador Binalf expressed his appreciation for the discussion, noting that it was worthwhile to engage with a true friend of Ethiopia who wishes nothing but prosperity and peace for the nation.

Ethiopian Embassy Hosts Cultural Showcase in Washington, D.C.

The Embassy of Ethiopia in Washington, DC in collaboration with the International DC Club organized a promotional event aimed at showcasing Ethiopia’s tourism attractions.

H.E. Binalf Andualem, Extraordinary and Plenipotentiary Ambassador of Ethiopia to the United States of America, delivered welcoming remarks, emphasizing Ethiopia’s deep-rooted cultural heritage. He highlighted the country’s UNESCO-recognized treasures, including the Obelisks of Axum, the rock-hewn churches of Lalibela, and the castles of Gondar, ancient walled city of Harar, the unique cultures of the Omo Valley, the otherworldly Danakil Depression, Simien & Bale mountains. He expressed gratitude to both the participants and the event organizers, emphasizing that cultural exchange plays a key role in fostering global relationships.

A large number of American visitors participated in the event, during which they were encouraged to write their names in Amharic (Ge’ez script) and familiarize themselves with the Ethiopian alphabet.

The event also showcased how traditional Ethiopian clothing is made from hand-woven fabric, along with a video presentation highlighting Ethiopia’s historical monuments and tourist attractions.

The program featured a traditional food and drinks, and the Ethiopian coffee ceremony as key components. It was reported that many of the guests who attended the event expressed a strong interest in visiting Ethiopia to experience its tourist attractions first hand.

በአሜሪካን ዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢንተርናሽናል ዲሲ ክለብ ጋር በመተባበር የኢትዮጵያን የቱሪዝም መስዕቦችን የሚያስተዋውቅ መድረክ አዘጋጀ።

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው ቅርሶች መካከል የአክሱም ሀውልት፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ ጥንታዊቷ የሐረር ከተማ፣ የሰሜን እና ባሌ ተራሮችን ጨምሮ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ሃብቶች በርካታ መሆናቸውን በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል። እንዲህ አይነት የባህል መድረኮች ዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ያለውን ጠቀሜታ በመግለጽ ተሳታፊዎችን እና አዘጋጆቹን አመስግነዋል።

በዝግጅቱ በርካታ አሜሪካውያን ጎብኚዎች የተሳተፉ ሲሆን ስማቸውን በአማርኛ (የግእዝ ፊደል) እንዲጽፉና የኢትዮጵያን ፊደሎች እንዲለማመዱ፣ የኢትዮጵያ የባህል ልብሶች ከተፈተለ ጥጥ እንዴት እንደሚሰሩ እንዲሁም የኢትዮጵያን ታሪካዊ ቅርሶችና የቱሪዝም ምስዕቦችን የሚያሳይ ቪዲዮ ለእይታ ቀርቧል፡፡

የኢትዮጵያ ባህላዊ ውዝዋዜ ትርኢት፣ ባህላዊ ምግብና መጠጦች፣ ባህላዊ የቡና አፈላል ስነስርዓት የዝግጅቱ አካል የነበሩ ሲሆን ዝግጅቱን ለመጎብኘት የመጡ እንግዶች የኢትዮጵያን የቱሪዝም መስዕቦችን በቀጣይ ወደ ኢትዮጵያ በመጓዝ ለመጎብኘት ፍላጎት ያደረባቸው መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት ይደግፋል − በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ

ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የአሜሪካ መንግስት እንደሚደግፍ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ አስታወቁ፡፡

ኢትዮጵያ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያስመዘገበች መሆኗንም አምባሳደሩ አረጋግጠዋል።

በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ እንደምትሰራም ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት እንደምትሰራ በአጽንኦት መግለጻቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋ እንዲመለስ በሰላማዊ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና ሰጥቶ በመቀበል መርህ እንደምትሰራ በተደጋጋሚ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ያስታወቁት ጉዳይ ነው።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በፈጣን ኢኮኖሚ እድገት ውስጥ ትገኛለች።

ሀገሪቱ ሰፊ የህዝብ ቁጥር ያላት እና ፈጣን ኢኮኖሚ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ያወሱት አምባሳደር ማሲንጋ፤ ይህ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚቀጥልም ትንበያ መኖሩን አመልክተዋል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በዓለም ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ ለመገንባት ያላትን ህልም ለማሳካት የባህር በር አማራጯን ማስፋት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው፤ በሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገውን ጥረት የአሜሪካ መንግስት የሚደግፈው መሆኑንም አረጋግጠዋል።

አምባሳደር ማሲንጋ እንዳብራሩት፤ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላም እና ፀጥታ ለማረጋገጥ አሜሪካ ከወሳኝ አጋሯ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ ትሰራለች።

ኢትዮጵያ ቀጣናው ወደ መረጋጋትና ሰላም እንዲመለስ አስተዋጽኦ እያደረገች መሆኑን አመልክተው፤ ከኢትዮጵያ ጋር በጋራ መስራት አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ጠንካራ አቋም መሆኑን አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ በቀጣናው ግዙፍ ብቻ ሳትሆን አቅም እና ተጽዕኖ ያላት ሀገር ነች ያሉት አምባሳደር ማሲንጋ፤ በቀጣናው መረጋጋትና ሰላም ለማስፈን ሀገራቱ በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

Ambassador Ervin Massinga: The U.S. Supports Ethiopia’s Peaceful and Diplomatic Efforts to Secure Sea Access

U.S. Ambassador to Ethiopia, Ervin Massinga, stated that the U.S. government supports Ethiopia’s peaceful and diplomatic efforts to gain access to the sea.

Ambassador Massinga also noted Prime Minister Dr. Abiy Ahmed’s strong commitment to pursuing sea access through peaceful and diplomatic means.

Highlighting Ethiopia’s large population and fast-growing economy, the ambassador expressed optimism that this growth will continue. He underlined the importance of broadening Ethiopia’s options for sea access to help realize the country’s vision of becoming a globally competitive economy.

He reaffirmed that the U.S. government supports Ethiopia’s peaceful diplomatic push for maritime access, recognizing its critical role in achieving sustainable development.

Ambassador Massinga also stated that Ethiopia is steadily returning to peace and stability, and emphasized America’s strong strategic interest in working with Ethiopia as a key player in the Horn of Africa.

He described Ethiopia not only as a large country but also as one with significant capacity and influence. He reiterated that countries in the region must work together to foster lasting peace and stability

Highlighting Ethiopia’s large population and fast-growing economy, the ambassador expressed optimism that this growth will continue. He underlined the importance of broadening Ethiopia’s options for sea access to help realize the country’s vision of becoming a globally competitive economy.

He reaffirmed that the U.S. government supports Ethiopia’s peaceful diplomatic push for maritime access, recognizing its critical role in achieving sustainable development.

Ambassador Massinga also stated that Ethiopia is steadily returning to peace and stability, and emphasized America’s strong strategic interest in working with Ethiopia as a key player in the Horn of Africa.

He described Ethiopia not only as a large country but also as one with significant capacity and influence. He reiterated that countries in the region must work together to foster lasting peace and stability.

#Ethiopia

#Ethiopian_News_Agency

#ኢዜአ

ክቡር አምባሳደር በስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ረዳት ፀሃፊ ጋር ተወያዩ

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱዓለም በስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ረዳት ፀሃፊ ቪንሴንት ዲ. ስፔራ ጋር በኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገናኝተው በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማስፈን እየተደረገ ያለውን ጥረት ጨምሮ በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሀሳብ የተለዋወጡ ሲሆን፣ ሁለቱ ሀገራት በትብብር ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም ገልጸዋል። ምክትል ረዳት ፀሃፊው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢኮኖሚያዊ ትብብር የሚሰጠውን ትኩረት አፅንዖት ሰጥተው የገለጹ ሲሆን፣ ክቡር አምባሳደሩ በበኩላቸው በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ሪፎርምና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ አጋርነት ለማጠናከር ያላቸውን ጠቀሜታ አስረድተዋል።

H.E. Ambassador Binalf Andualem met with Vinny D. Spera, the Deputy Assistant Secretary of the Bureau of African Affairs of the State Department at the Ethiopian Embassy and discussed the ongoing efforts to achieve lasting peace in Ethiopia. They also exchanged opinions on regional and global issues and committed to coordinating their actions. The Deputy Assistant Secretary emphasized the current administration’s focus on economic cooperation, while the Ambassador provided an overview of the reforms taking place in Ethiopia and their importance for strengthening the economic partnership between the two countries.

The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia

MFAEthiopia Amharic የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

SelectUSA Investmenet Summit-2025 ላይ ለመሳተፍ ከኢትዮጵያ የመጡ ባለሀብቶች ጋር ውይይት ተካሄደ፤

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም SelectUSA Investmenet Summit-2025 ላይ ለመሳተፍ ከኢትዮጵያ የመጡ ባለሀብቶች ጋር በኤምበሲያችን ውይይት ያካሂዱ ሲሆን በመድረኩ የኢትዮ-አሜሪካ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ ፕሬዝዳንትና ቦርድ አባላት፣ የአሜሪካ ኮሜርስ ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ተጠባባቂ ዳይሬክተር እንዲሁም በአሜሪካ የዲ.ኤም.ቪና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልድ ኢትዮጵያዊያን ባለሀብቶች እና ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች፣ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላለፍዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ለመጣው የባለሃብት ልዑክ እና እዚህ አሜሪካን አገር ለሚኖሩ ባላሃብቶች ይህንን አጋጣሚ በአግባቡ በመጠቀም እና ትርጉም ያለው ግንኙነት በመመስረት በሀገር ቤት ያለውን የኢንቨስትመንትና የገበያ እድሎችን ለመጠቀም በር የሚከፍት መሆኑን ክቡር አምባሳደሩ በመክፈቻ ንግግራቸው አንስተዋል፡፡

የኢትዮ-አሜሪካ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ እና የአሜሪካ ኮሜርስ ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች የአሜሪካ ባለሃብቶች ወደ ሀገራችን ገብተው ያለውን የንግድና የኢንቨስትመንት አማራጮችን መጠቀም እንዲችሉ ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን ይህንኑ ለማገዝ ኤምባሲው እንደ ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል መሆኑን ገልፀዋል።

በኤምባሲው የተካሄደው ይህ ዝግጅት ከኢትዮጵያ የመጣው የባለሃብት ልኡካን ቡድን አሜሪካ ከሚገኙ አቻዎቻችው ጋር ግንኙነት በመመስረት ትስስር መፍጠር እንዲችሉና የነበረውን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ መድረክ ነው፡፡

Meeting Held with Ethiopian Investors Attending SelectUSA Summit-2025

H.E. Binalf Andualem, Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of Ethiopia to the United States, hosted a discussion at the Embassy with Ethiopian investors participating in the SelectUSA Investment Summit 2025. During the forum, the Ambassador extended a warm welcome to the President and Board Members of the Ethio-American Chamber of Commerce, the Acting Director of African Affairs at the U.S. Department of Commerce, Ethiopian and Ethiopian-American investors residing in the DMV area, and other invited guests.

In his opening remarks, the Ambassador emphasized that the event creates an opportunity for the investor delegation from Ethiopia and those residing in the United States to build meaningful relationships and effectively capitalize on the investment and market opportunities available in Ethiopia.

The Ethio-American Chamber of Commerce and the African Affairs Office of the U.S. Department of Commerce encouraged American investors to explore the trade and investment opportunities available in Ethiopia and emphasized that the Embassy serves as a vital bridge to facilitate this engagement.

The event held at the Embassy served as a forum for the investor delegation from Ethiopia to connect with their American counterparts and to strengthen existing relationships.

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ጋር ተወያዩ፤

ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ዋሽንግተን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ጋር በሚሲዮኑ በመገኘት ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በሚሲዮኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊተገበሩ በሚገባቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ካነሷቸው ነጥቦች መሃከል ዲፕሎማቱና መላው ሰራተኛ በፖለቲካ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ፣ ሃብት ማፍራት፣ ወጪ ቅነሳ እንዲሁም ዲያስፖራ ጉዳዮችና ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በቡድን መንፈስ በመንቀሳቀስ የሚቆጠርና ውጤት ማስመዝገብ ላይ ትኩረት በማድረግ መሰራት እንደሚገባው አንስተዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የልማት እንቅስቃሴዎችን በተገኘው አጋጣሚ ለአሜሪካ መንግስትና ባላብቶች እንዲሁም ለዲያስፖራው ማህበረሰብ በማስተዋወቅ የአገራችንን ገጽታ መገንባትና ኢንቨስተሮች ወደ አገራችን ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ በማስቻል ረገድ ትልቅ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።

በመጨረሻም ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሰፋ ያለ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢቨንትስ ዲሲ ጋር ውይይት አደረገ

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ ታላላቅ ስብሰባዎችን፣ መዝናኛዎችን፣ ስፖርታዊ እና ባህላዊ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ኢቨንትስ ዲሲ ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስ ጌትስ እና ሎሎች አመራር አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።

ክቡር አምባሳደሩ ባደረጉት ንግግር የአዲስ አበባ እና የዋሽንግተን ዲሲ ከተሞች ያላቸው እህትማማች ግንኙነት ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከማጠናከር ባሻገር በሁለቱ ዋና ከተሞች መካከል ያለውን ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ተቋማዊ ትብብሮችን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። ክቡር አምባሳደሩ አክለውም ኢትዮጵያ በቅርቡ በአይነቱ ልዩ የሆነና አለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኮንቬሽን ማዕከል ግንባታ አጠናቃ ስራ ያስጀመረች መሆኑና ይህ እጅግ ዘመናዊ ኮንቬሽን ማዕከል ኢትዮጵያ አለምአቀፍ ኮንቬንሽኖችን፣ ኤግዚቢሺኖችንና ባህላዊ አውደ ርዕዮችን ከማስተናገድ አንጻር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገራት እመርታ መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም ወደ ስራ እየገባ ያለው አዲስ አለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ስኬታማ ከማድረግ አንጻር እንደ ኢቨንትሰ ዲሲ ካሉ በመስኩ ልምድ ካካበቱ ተቋማት ልምድ ልውውጥ ማድረግና በትብብር መስራት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢቨንትስ ዲሲ ፕሬዝዳንትም በበኩላቸው ተቋማቸው ያለውን ልምድ ለማካፈል እና በሚፈለገው ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

በሌላ ጉዳይ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ያቀኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ በዚሁ ውይይት ላይ የተገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ የአለምአቀፍ ስብሰባዎች ማዕከል እየሆነች መምጣቷንና በተለይም አዲስ አለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል አዲስ ከመሆኑ አንጻር ከኢቨንትስ ዲሲ ልምዶችን ቀምሮ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

The Embassy of Ethiopia held discussions with Events DC

Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to the US H.E Binalf Andualm held a discussion with Ms. Angie M. Gates, President and CEO of Events DC, an organization renowned for hosting major conferences, entertainment, sports, and cultural events in Washington, DC as well as with members of the management team.

In his speech, the Ambassador emphasized that, in addition to enhancing diplomatic relations between the sister cities of Addis Ababa and Washington, DC, the initiative will also strengthen cultural, economic, and institutional cooperation between the two capitals. He added that Ethiopia has recently completed the construction of a state-of-the-art Addis International Convention Center (AICC) that is unique in its design and built to international standards, which is now operational.

In addition, the Ambassador stated that to ensure the success of the newly operational international convention center, it is essential to exchange experiences and collaborate with established institutions in the field, such as Events DC.

The President and CEO of Events DC, for her part, expressed her institution’s readiness to share its experience and collaborate in any way necessary.

While in Washington, DC for a separate engagement, the State Minister of Foreign Affairs of Ethiopia, H.E. Ambassador Berhanu Tsegaye, joined the discussion. He highlighted Ethiopia’s emergence as a hub for international conferences and stressed the value of applying Events DC’s best practices to support the success of the Addis International Convention Center.