በኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሞሐመድ እንድሪስ የሚመራ ልዑካን ቡድን በሰሜን አሜሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር የዳያስፖራ ዲፕሎማሲና ሁለንተናዊ ተሳትፎ ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ለመመካከር ቆይታ ያደርጋል።
ልዑካን ቡድኑ በዋሺንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገኝተው በዳያስፖራ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲሁም በኤምባሲው የሚሰጡ የዳያስፖራ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በዛሬው እለት ውይይት አካሂደዋል።
ክቡር አምባሳደር ስለሺ የኤምባሲው ሰራተኞች በተገኙበት ለልኡካን ቡድኑ በኤምባሲው የተከናወኑ የፖለቲካ፣ የቢዝነስ፣ የዳያስፖራ ዲፕሎማሲ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንዲሁም በዳያስፖራ የአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ዙሪያ ዝርዝር ገለፃ አድርገዋል።
ባለፉት አመታት በአገራችን የገጠሙ ችግሮችን ለመሻገር በሚደረገው ጥረትም ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሀገራቸው ጎን በመሆን በሀገራችን ላይ ተላልፈው የነበሩ አግባብ ያልሆኑ ውሳኔዎችን ለመቀልበስ በርካታ ርብርብ ሲደረግ እንደነበር ክቡር አምባሳደር ስለሺ ባደረጉት ገለጻ ጠቅሰዋል፤ ከዚሁ ጋር ተያይዞ የዳያስፖራ አደረጃጀቶችን በማደራጀትና በማጠናከር ለሀገራዊ ጥሪ ፕሮጀክቶች፣ በጦርነቱ አማካኝነት የተጎዱ የአገራችን ክፍሎች መልሶ ግንባታ ድጋፎችን በመሰብሰብ፣ በግጭት ምክንያት የተጎዱ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋምና የወደሙ መሰረተ-ልማቶችን መልሶ ለመገንባት፣ ለገበታ ለትውልድ ፕሮጀከት እንዲሁም ለበጎ አድራጎት ስራዎች ከዳያስፖራው ጋር በመሆን የተሰሩ ስራዎችን አብራርተዋል።

የልኡካን ቡድን በዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው እያደረገ ባለው ቆይታም በዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ ማዕከል ጉብኝት አድርጓል።
ከተቋቋመ 20ዓመታትን ያስቆጠረው በዋሺንግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ ማዕከል ለኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ የጤና ሽፋን አገልግሎት፣ የትምህርት እድሎችን ማመቻቸት፣ የአቅም ግንባታ፣ ከማህበረሰቡ የሚነሱ ችግሮችን ለመፍታት፣ እንዲሁም በርካታ ማህበራዊ ስራዎችን ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በማቅረብ አገልዕግሎቶችን እንደሚሰጥ የማእከሉ ሀላፊ የልኩካን ቡድኑ ባደረጉት ጉብኝት ገለጻ ሰጥቷል።
ማህበረሰቡን የማዕከሉ አባል በማድረግ የሚያቀርበውን አገልግሎት የልኡካን ቡድኑ አበረታተው ማዕከሉ የነዋሪዎችን ህይወት ለመቀየር በርካታ እድሎችን በማመቻቸት በተለይም የማእከሉ አባል ሆነው የጤና አገልግሎት በማመቻቸት ተጠቃሚዎች የጤና ሽፋን እንዲያገኙ የሚያደርገው ስራ እጅግ የሚበረታታ እንደሆነ ጠቅሰው የማእከሉን ከ20 አመታት በላይ ያስቆጠረ አገልግሎት ለማስቀጠል ስትራቴጂክ የሆኑ እቅዶችን በማውጣትና በመቀናጀት ቀጣይነቱን ማረጋገጥ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሞሐመድ እንድሪስ ገልጸዋል።
ከማህበረሰቡ የሚነሱ በርካታ ጥያቄዎች እንዳሉ የማእከሉ ሀላፊ በጉብኝት ወቅቱ ያነሱ ሲሆን ይህንንም ለመፍታት ከኤምባሲው ጋር በመተባበር ብዙ ስራዎችን ለማከናወን የተለያዩ የስትራቴጂክ እቅዶችን ማዘጋጀቱን ለልኡካን ቡድኑ አብራርቷል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአሜሪካ ምክር ቤት አባል ትሬንት ኬሊን በጽ/ቤታቸው ተቀበሉ

( ሰኔ 27 ቀን 2015ዓ.ም) የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን የአሜሪካ ምክር ቤት አባል ትሬንት ኬሊ ዛሬ (ሰኔ 27/2015 ዓ.ም) በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የተከበሩ ኬሊን ውይይት የኢትዮ አሜሪካ ወዳጅነት የበለጠ በሚጠናከርበት እና የአፍሪካ ቀንድ የሠላም እና ደህንነት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
የምክር ቤቱ ባለፈው ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ በኃላ ያደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝት እንደሆነ ጠቅሰው ብዙ ጉዳዮች በበጎ ሁኔታ መለወጣቸውን መታዘብ እንደቻሉ ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ ሰላም እንዲመጣ እየወሰደ ያለውን በጎ ዕርምጃ አሜሪካ እንደምትገነዘብ ጠቅሰው ከሰብአዊ መብት ጋር በተያያዘ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱ ግንኙነቱ ለማጠናከር ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡

ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ በመስጠት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የዳግም ግንባታና የመልሶ ማቋቋም ዕቅዶችን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “የ21ኛው ክፍለ ዘመን ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የባለብዙ ወገን ልማት ባንኮችን ሞዴል ማሻሻል” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ውይይት ላይ ተሳተፉ

አዲስ አበባ ሰኔ 15/2015(ኢዜአ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “የ21ኛው ክፍለ ዘመን ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ የባለብዙ ወገን ልማት ባንኮችን ሞዴል ማሻሻል” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ውይይት ላይ ተሳትፈዋል።

በፈረንሳይ ፓሪስ በተካሄደው አዲስ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስምምነት ጉባኤ ላይ አራት ነጥቦችን አንሥተው አጽንዖት ሰጥተዋል።

ነጥቦቹም:-

1) ከዚህ በፊት ቃል የተገቡ ስምምነቶችን መተግበር እንደሚያስፈልግ
2) የኮንሴሽናል ፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ
3) ወደ አረንጓዴ ልማት ሽግግር ለማድረግ ለሚያስፈልገው የገንዘብ ድጋፍ ጠንካራ ዘዴ መፍጠር እና
4) የዕዳ ቀውስን ማቆም መሆናቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።

DPM and FM Demeke Urges Equitable and Reasonable Use of the Nile

During the “2nd Afri-Run High-Level Forum on Equitable and Reasonable Utilisation of Transboundary Watercourses in Africa” held today at the Skylight Hotel in Addis Ababa, Deputy Prime Minister and Foreign Minister Demeke Mekonnen Hassen urged riparian states for an equitable and reasonable use of the Nile River. The Forum was conducted under the theme “African Resources for African Prosperity in the New Age”. The second leg of the forum will be conducted tomorrow (23 June).

In his keynote address DPM and FM Demeke noted, lack of political will and hegemonic tendencies over shared resources immensely contribute to little or no cooperation. He added, these challenges will continue to stand against our shared aspirations of ensuring sustainable development.

He said, it is high time that we redouble efforts to deal with the challenges building on the great strides we have made in the past to ensure equitable and reasonable use of transboundary resources. The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is an exemplary initiative that champions equitable and reasonable use, he added.

H.E. Ambassador Seleshi Bekele held a fruitful discussion with Mr. Nick Lagunowich, Pfizer’s

Yesterday, H.E. Ambassador Seleshi Bekele held a fruitful discussion with Mr. Nick Lagunowich, Pfizer’s Global President of Emerging Markets. A team of Pfizer’s executives will travel to Ethiopia to discuss the implementation of its ‘Accord for a Healthier World’ that aims to provide medicines and vaccines to 45 lower-income countries, including Ethiopia, on a not-for-profit basis. H.E. Ambassador Seleshi Bekele said the collaboration would help many people in these countries to get access to high-quality & effective medications

ክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለ ከበድር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሙስሊም ድርጅት ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም የበድር ኢትዮጵያ ተወካዮች በቅርቡ ከእስልምና እምነት ተቋማት እና ከመኖሪያ ቤቶች ጋር በተገናኘ በተለይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ተከስተዋል ያሏቸውን ችግሮች አንስተዋል።

በድር ኢትዮጵያ ህገ-ወጥነተን እንደማይደግፍ፤ ይሁንና የሚወሰዱ እርምጃዎች ህዝቡን አደጋ ላይ በማይጥል፣ በውይይት እና ወደ ቅሬታ በማያስገባ መልኩ እንዲሆን ጠይቀዋል።

ድርጅቱ በቀጣይም አባላቱን በማስተባባር ለአገር ልማት፣ ሰላምና መልሶ ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል።

ክቡር አምባሳደር ስለሺ በበኩላቸው የተነሱትን ጥያቄዎች እንደሚገነዘቡ፣ በድር ኢትዮጵያ አገራችን ኢትዮጵያ በገጠሟት ፈተናዎች ሁሉ አባላቱን አስተባብሮ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ድጋፍ በማድረግ ላሳየው አጋርነት አመስግነዋል። ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

በድርጅቱ ተወካዮች በኩል የተነሱ ጥያቄዎችን እና በጽሁፍ የቀረቡ መልዕክቶችን ለሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እንደሚያደርሱም ቃል ገብተዋል።

The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia
Dr Eng Seleshi Bekele

ክቡር አምሳሳደር ስለሺ በቀለ በአሜሪካ ከሚገኙ ከ36 በላይ የዳያስፖራ አደረጃጀት ኃላፊዎችና ተወካዮች ጋር ሰኔ 8/2015 ዓ.ም ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱም በአገራችን ዘላቂ ሰላም ለመገንባት እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች፣ የገጠሙ ፈተናዎችና መፍትሄዎቻቸው፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅታዊ ሁኔታ፣ በአዲስ አበባ ዙሪያ ከቤተ-እምነቶች እና መኖሪ ቤቶች ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች፣ በአገራችን ሰላምና አንድነት የዳያስፖራው ተሳትፎ፣ በሁለትዮሽ ግንኙነትና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር።

አምባሳደር ስለሺ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በአገራችን ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን መንግስት ሁሉን አቀፍ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የተወሰዱት እርምጃዎች ለአብነት አንስተዋል።

ከእምነት ተቋማትና ከመኖሪያ ቤቶች መፍረስ ጋር ተያይዞ ጥያቄዎች ለኤምባሲውም በአካልና በተለያዩ መንገዶች መቅረባቸውን ጠቁመው ህግን በማስከበር ሂደት ካለፉት ክፍተቶች በመማር መንግስት ህዝቡን ያመከለ አካሄዶችን እንደሚያስቀድም ጠቅሰዋል።

አገራችን ባለፉት ጥቂት አመታት ከውስጥም ከውጭም በገጠሟት ፈተናዎች ሁሉ ዳያስፖራው ላበረከተው ሁሉን አቀፍ ገንቢ አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

ወቅቱ አገራችን ከነበሩባት ፈተናዎች ወጥታ ወደምትታወቅበት ሰላምና ፈጣን ልማት እንድትገባ ልዩነቶችን ወደጎን በመተው ለትውልድ የሚሻገር አሻራ ለማሳረፍ ሁለም ሊረባረብ እንደሚገባም አምባሳደር ስለሺ ተናግረዋል።

በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ የአረብ ሊግ በተደጋጋሚ የሚያወጣቸው መግለጫዎችና አፍራሽ እንቅስቃሴዎች ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅሟን ሳታስደፍር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ ከተመሰረተው አቋሟ ዝንፍ እንደማትል ገልጸዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም መንግስት ህግን ለማስከበር የሚወስዳቸው እርምጃዎች ንጹሃንን ለእንግልት የማያጋልጡ እንዲሆኑ፣ ለውይይት ቅድሚያ እንዲሰጥ፣ በዜጎች ላይ ኢ-ሰብዓዊ እርምጃ የወሰዱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፣ የመረጃ ፍሰት እንዲጎለብት እና ሌሎች ሃሳቦች ያነሱ ሲሆን የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንድሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

ክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለ ከበድር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሙስሊም ድርጅት ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም የበድር ኢትዮጵያ ተወካዮች በቅርቡ ከእስልምና እምነት ተቋማት እና ከመኖሪያ ቤቶች ጋር በተገናኘ በተለይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ተከስተዋል ያሏቸውን ችግሮች አንስተዋል።በድር ኢትዮጵያ ህገ-ወጥነተን እንደማይደግፍ፤ ይሁንና የሚወሰዱ እርምጃዎች ህዝቡን አደጋ ላይ በማይጥል፣ በውይይት እና ወደ ቅሬታ በማያስገባ መልኩ እንዲሆን ጠይቀዋል። ድርጅቱ በቀጣይም አባላቱን በማስተባባር ለአገር ልማት፣ ሰላምና መልሶ ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። ክቡር አምባሳደር ስለሺ በበኩላቸው የተነሱትን ጥያቄዎች እንደሚገነዘቡ፣ በድር ኢትዮጵያ አገራችን ኢትዮጵያ በገጠሟት ፈተናዎች ሁሉ አባላቱን አስተባብሮ የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ድጋፍ በማድረግ ላሳየው አጋርነት አመስግነዋል። ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። በድርጅቱ ተወካዮች በኩል የተነሱ ጥያቄዎችን እና በጽሁፍ የቀረቡ መልዕክቶችን ለሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እንደሚያደርሱም ቃል ገብተዋል።

JOINT STATEMENT BY USAID AND MINISTRY OF FOREIGN AFFAIRS OF THE FEDERAL DEMOCRATIC REPUBLIC OF ETHIOPIA

Mayor Adanech concludes her successful working visit in Washington D.C.

H.E Adanech Abiebie, Mayor of Addis Ababa, concludes her fruitful working visit in Washington D.C.
In her weeklong Washington D.C mission, The Mayor held a series of bilateral discussions, field visits, experience sharing seminars and diaspora engagements.
She had a candid bilateral conversation with her Washington D.C. counterpart, Mayor Muriel Bowser, on ways of implementing the Sister-City Agreements signed in 2019.
The Mayors agreed to establish a working group aimed at invigorating the gaps and opportunities in terms of implementing the agreement and way forward.
H.E Ambassador Seleshi mentioned that the Embassy will continue bridging the offices of the two cities.
An experience sharing consultation forum was also held between the cities sectoral offices such as Health, educations, planning, economic development bureaus. In this forum, the respective offices presented their best practices and lessons to be taken.

Washington D.C sectoral offices vowed to provide capacity building trainings to Addis Ababa City experts on several fronts.
The Mayor and her Delegation paid several field visits including the capital river front redevelopment projects around Navy yard, D.C Water and recycling projects built by public and private partnerships.
In her last day of Washington D.C mission H.E Mayor Adanech Abiebie held a candid discussion with DMV area Ethiopia Diaspora Business Community where 200,000 USD was raised for the “Dine for Generation” project.
Mayor Adanech elaborated the conducive investment opportunities in Addis Ababa in the areas of technology, construction, health, hospitality, education and several others.
She also lauded Embassy of Ethiopia, Washington, D.C. for facilitating bilateral discussions, field tours in collaboration with Mayor office of D.C and organizing a fruitful diaspora engagements in coordination.
Prior to traveling to D.C, Mayor Adanench and her Delegation had a productive engagement with the City of Denver which was showcased by the signing of a Sister City Agreement with Addis Ababa.