በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ለአገራችን ሰላም፣ልማትና አንድነት ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ አስታወቁ።
በዋሽንግተን የኢፌዲሪ ኤምባሲ የ2016 ዓም የዘመን መለወጫ ዋዜማ በዓልን በዋሺንግተን ዲሲና አካባቢው ከሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት አክብሯል።በአሜሪካ የኢፌዲሪ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ባስተላለፉት መልዕክት አዲሱ ዓመት ካሳለፍናቸው ስኬቶችና ፈተናዎች ትምህርት በመቅሰም ለአገር የሚበጁትን እንደ ወረት ይዘን ለአገራችን ልማትና አንድነት ቃል የምንገባበት ወቅት ነው ብለዋል።መጪውን አመት […]
