የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ጋር ተወያዩ፤

ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ዋሽንግተን ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች ጋር በሚሲዮኑ በመገኘት ውይይት ያካሄዱ ሲሆን በሚሲዮኑ ትኩረት ተሰጥቶ ሊተገበሩ በሚገባቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ካነሷቸው ነጥቦች መሃከል ዲፕሎማቱና መላው ሰራተኛ በፖለቲካ ዲፕሎማሲ፣ ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ፣ ሃብት ማፍራት፣ ወጪ ቅነሳ እንዲሁም ዲያስፖራ ጉዳዮችና ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በቡድን መንፈስ በመንቀሳቀስ የሚቆጠርና ውጤት ማስመዝገብ ላይ ትኩረት በማድረግ መሰራት እንደሚገባው አንስተዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የልማት እንቅስቃሴዎችን በተገኘው አጋጣሚ ለአሜሪካ መንግስትና ባላብቶች እንዲሁም ለዲያስፖራው ማህበረሰብ በማስተዋወቅ የአገራችንን ገጽታ መገንባትና ኢንቨስተሮች ወደ አገራችን ገብተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ በማስቻል ረገድ ትልቅ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው አሳስበዋል።

በመጨረሻም ከሚሲዮኑ ሰራተኞች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሰፋ ያለ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢቨንትስ ዲሲ ጋር ውይይት አደረገ

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በዋሽንግተን ዲሲ የተለያዩ ታላላቅ ስብሰባዎችን፣ መዝናኛዎችን፣ ስፖርታዊ እና ባህላዊ ዝግጅቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ኢቨንትስ ዲሲ ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስ ጌትስ እና ሎሎች አመራር አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።

ክቡር አምባሳደሩ ባደረጉት ንግግር የአዲስ አበባ እና የዋሽንግተን ዲሲ ከተሞች ያላቸው እህትማማች ግንኙነት ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከማጠናከር ባሻገር በሁለቱ ዋና ከተሞች መካከል ያለውን ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ተቋማዊ ትብብሮችን የሚያጠናክር መሆኑን ገልጸዋል። ክቡር አምባሳደሩ አክለውም ኢትዮጵያ በቅርቡ በአይነቱ ልዩ የሆነና አለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኮንቬሽን ማዕከል ግንባታ አጠናቃ ስራ ያስጀመረች መሆኑና ይህ እጅግ ዘመናዊ ኮንቬሽን ማዕከል ኢትዮጵያ አለምአቀፍ ኮንቬንሽኖችን፣ ኤግዚቢሺኖችንና ባህላዊ አውደ ርዕዮችን ከማስተናገድ አንጻር ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገራት እመርታ መሆኑን ተናግረዋል።

አያይዘውም ወደ ስራ እየገባ ያለው አዲስ አለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል ስኬታማ ከማድረግ አንጻር እንደ ኢቨንትሰ ዲሲ ካሉ በመስኩ ልምድ ካካበቱ ተቋማት ልምድ ልውውጥ ማድረግና በትብብር መስራት ተገቢ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢቨንትስ ዲሲ ፕሬዝዳንትም በበኩላቸው ተቋማቸው ያለውን ልምድ ለማካፈል እና በሚፈለገው ሁሉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

በሌላ ጉዳይ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ያቀኑት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ በዚሁ ውይይት ላይ የተገኙ ሲሆን ኢትዮጵያ የአለምአቀፍ ስብሰባዎች ማዕከል እየሆነች መምጣቷንና በተለይም አዲስ አለምአቀፍ ኮንቬሽን ማዕከል አዲስ ከመሆኑ አንጻር ከኢቨንትስ ዲሲ ልምዶችን ቀምሮ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

The Embassy of Ethiopia held discussions with Events DC

Ambassador Extraordinary and Plenipotentiary of the Federal Democratic Republic of Ethiopia to the US H.E Binalf Andualm held a discussion with Ms. Angie M. Gates, President and CEO of Events DC, an organization renowned for hosting major conferences, entertainment, sports, and cultural events in Washington, DC as well as with members of the management team.

In his speech, the Ambassador emphasized that, in addition to enhancing diplomatic relations between the sister cities of Addis Ababa and Washington, DC, the initiative will also strengthen cultural, economic, and institutional cooperation between the two capitals. He added that Ethiopia has recently completed the construction of a state-of-the-art Addis International Convention Center (AICC) that is unique in its design and built to international standards, which is now operational.

In addition, the Ambassador stated that to ensure the success of the newly operational international convention center, it is essential to exchange experiences and collaborate with established institutions in the field, such as Events DC.

The President and CEO of Events DC, for her part, expressed her institution’s readiness to share its experience and collaborate in any way necessary.

While in Washington, DC for a separate engagement, the State Minister of Foreign Affairs of Ethiopia, H.E. Ambassador Berhanu Tsegaye, joined the discussion. He highlighted Ethiopia’s emergence as a hub for international conferences and stressed the value of applying Events DC’s best practices to support the success of the Addis International Convention Center.

ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን አስመልክቶ የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ።

በአሜሪካ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ በተለያዩ ስቴቶች ከሚኖሩ የዳያስፖራ አደረጃጀት፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና በውሃ ዙሪያ የሚሰሩ ተቋማት አደረጃጀቶች አመራርና አባላት ጋር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ውይይት አካሂደዋል፡፡

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የህዳሴ ግድብ በተለያየ ፈተና ውስጥ አልፎ ዛሬ እዚህ በመድረሱ እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ይህ ፕሮጀክት የኢትየጵያን የመበልጸግ ፍላጎት እውን ከሚያደርጉ የልማት ፕሮጀክቶች አንዱ በመሆኑ የቀረውን ሁለት በመቶ ለማጠናቀቅ እንደዚህ ቀደሙ አሻራችንን ለማስቀመጥ ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡

አክለውም አገራችን እንድትበለጽግና ብሔራዊ ጥቅሟ እንዲረጋገጥ እጅ ለእጅ ተያይዘን መስራት እንደሚያስፈልግ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ግድቡ አሁን የደረሰበትን 98 በመቶ ለመድረስ ያለፈውን በጎ አጋጣሚና ተግዳሮቶች ላይ ሰፋ ያለ ገለፃ አድርገዋል፡፡

ገለጻውን መነሻ በማድረግ ከዳያስፖራው ለተሰጡ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ምላሽ የተሰጠ ሲሆን ዳያስፖራው ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡

ለግድቡ ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ዙር ገንዘብ ማሰባሰብ ከተጀመረ ጀምሮ 28,338 የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም ቅዳሜ ሜይ 10/2025 በተካሄደው ገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ 4760 ዶላር በድምሩ 33,098 ገቢ የተደረገ ሲሆን 21,810 ዶላር በእለቱ ቃል ተገብቷል፡፡

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ

ክቡር አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአሜሪካን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ገለጻ ለመስጠት እ.ኤ.አ. ሜይ 8 ቀን 2025 በጠሩት መድረክ ላይ ተሳትፎ አድርገዋል። በወቅቱም ክቡር አምባሳደሩ ከአሜሪካን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳኡ ጋር በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዙሪያ ሀሳብ ተለዋውጠዋል። ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየታየ ላለው አጠቃላይ ለውጥ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል። ክቡር አምባሳደሩ በበኩላቸው የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ያለበትን ሁኔታ አስመልክቶ ከምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጋር የተለዋወጧቸው ሀሳቦች በቀጣይ በተደራጀ መልኩ ለሚደረጉ መስተጋብሮች አጋዥ እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።

H.E. Ambassador Binalf Andualem took part in an event organized by U.S. Secretary of State Marco Rubio for a briefing on the current State of the Administration on May 8, 2025. During the event, Ambassador Binalef met with Christopher Landau, the Deputy Secretary of State of the U.S., and they exchanged ideas. The Deputy Secretary acknowledged the overall improvements in Ethiopia and expressed commitment to working together. Ambassador Binalf conveyed his confidence that their discussion on the state of the relationship between Ethiopia and the United States will serve as a foundation for future structured engagements

የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በሜኔሶታ ከክልሉ ተወላጆች ጋር ውይይት አደረጉ

እ.ኤ.አ. ሜይ 3 ቀን 2025 የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ አለሚቱ ኡመድ በአሜሪካ ሜኔሶታ ግዛት ነዋሪ ከሆኑ የክልሉ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ጋር በክልሉ እየተካሄደ ባለው የልማት ስራዎች እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።

ርዕሰ መስተዳድሯ በክልሉ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ እና እየተካሄደ ስላለው የልማት እንቅስቃሴ እንዲሁም ከዳያስፖራው ምን እንደሚጠበቅ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በክልሉ ያለው የሰላም ሁኔታ በእጅጉ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ የተሻለ ሁኔታም የክልሉን ልማት ለማፋጠን እና ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ መሰረት እንደሆነ ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር ዳያስፖራው በክልሉ እየተካሄደ ያለውን ልማት መደገፍ እንደሚገባው እና በኢንቨስትመንትም መሳተፍ እንዳለበት ተናግረዋል።

በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በተወካያቸው አቶ ተራመድ አዳነ አማካኝነት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ስለክልላቸው ብሎም ስለሀገራቸው ትክክለኛ መረጃዎችን በማግኘት እየተካሄደ ባለው የልማት እንቅስቃሴ ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ እንዲህ አይነት መድረክ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው መሆኑን ጠቅሰው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግንባታ ከ98 በመቶ በላይ መጠናቀቁን፤ በዚህም ሂደት በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት ተሳትፎ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው ካሉ በኋላ በዚህ ረገድ የጋምቤላ ኮሚኒቲ አደረጃጀት ተሳትፎ ከፍተኛ እንደነበረ በመጥቀስ በቀጣይ ግድቡ ተጠናቆ ሪቫን እስክንቆርጥ ድረስ የሚቻላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

በውይይቱ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በቂ ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ዳያስፖራው በክልሉ ለተጀመሩ የልማት ስራዎች ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ

አምባሳደር ብናልፍ አንዱአለም በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ሴናተር ቴድ ክሩዝ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ። ክቡር አምባሳደሩ ከሴናተሩ ጋር ሲገናኙ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን በዚህ ውይይታቸውም በአፍሪካ ንኡስ ኮሚቴ ሥራ እንዲሁም ንኡስ ኮሚቴው አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ግንኙነት ከማሳደግ አንጻር ባለው ሚና ላይ ተወያይተዋል። ሁለቱም ወገኖች በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር የበለጠ ተቀራርበው ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። ውይይታቸውም በዋና ዋና የጋራ ጉዳዮች እና በተለያዩ ዘርፎች ትብብርን ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ነበር።

Ambassador Binalef Andualem met with Senator Ted Cruz, who chairs the Africa subcommittee of the Senate Foreign Relations Committee. This meeting, their second, underscored a commitment to ongoing communication. They exchanged views on the work of the Africa subcommittee and its role in enhancing U.S.-Africa relations. Both parties expressed a strong desire to collaborate more closely to strengthen the bilateral relationship between the United States and Ethiopia. Their discussions focused on key areas of mutual interest and the potential for increased cooperation across various sectors.

“ሠላም ፍትህና ዕድገት ለኢትዮጵያ” ከተሰኘ የዳያስፖራ ምሁራን ህብረት ጋር ውይይት ተካሄደ

“ሰላም፣ ፍትህ እና ዕድገት ለኢትዮጵያ” የተሰኘ የዳያስፖራ ምሁራን ህብረት አባላት የካቲት 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ከክቡር አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በበይነ-መረብ መድረክ ውይይት አደረጉ።
በውይይቱ ወቅት የህብረቱ አባላት በትኩረት ካነሱዋቸው ጉዳዮች መካከል በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵየዊያን ለሀገራቸው በእውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና አቅማቸው በሚፈቅደው ሁሉ ለአገራቸው ሰላምና እድገት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚገባቸው፣ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ አንዲፈቱ የሁሉም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ርብርብ ወሳኝ መሆኑን፣ አደረጃጀታቸው በቀጣይ የዳያስፖራው ማህበረሰብ አባላትን በማስተባበር ከሀገሪቱ ልማት ጎን መቆም ዋነኛ ዓላማቸው መሆኑን ያሳወቁት ተሳታፊዎቹ፣ በአገራችን የተከሰቱ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጽኑ እምነታቸው መሆኑን ከመግለጽ ባሻገር ለተግባራዊነቱም እንደሚንቀሳቀሱ ገልጸዋል።

ክቡር አምባሳደሩ በበኩላቸው የህብረቱ አባላት ለሰላም ያላቸውን ተነሳሽነት አድንቀው መንግስት ሁልጊዜም ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሠራ መሆኑን በመግለጽ፣ ከህብረቱ አባላት በአስተያየትና ጥያቄ መልኩ በተነሱ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ዝርዝር ማብራሪያና ምላሽ ከሰጡ በኋላ ኤምባሲው ሁለንተናዊ የዳያስፖራ ተሳትፎን ለማረጋገጥ በቀጣይ ከማህበሩ አባላት ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት ገልጸውላቸዋል።

The official transfer of “Tsehay” by the Italian government is a cause for great pride for Ethiopians!

Today is a day of great pride for Ethiopians as we celebrate the official handover of “Tsehay” by the Italian Government. I extend my immense gratitude to Prime Minister Giorgia Meloni for her support over the past year in facilitating its return.

“Tsehay” is the first aircraft built in Ethiopia in 1935, under the collaborative efforts of the German engineer and pilot of the emperor, Herr Ludwig Weber, and Ethiopian individuals of that era.

PM Abiy Ahmed has joined Italy-Africa Summit

PM Abiy Ahmed has joined other African leaders at the Italy-Africa Summit hosted by Italian PM Giorgia Meloni. The summit is being held under the theme ‘a bridge for a common growth’. During the summit, Italy’s proposed ‘Mattei Plan’ for Africa will be discussed.

Prime Minister Abiy Ahmed has been awarded the prestigious FAO Agricola Medal

In a ceremony hosted by the United Nations Food and Agriculture Organization in Rome, Italy, Prime Minister Abiy Ahmed has been awarded the prestigious FAO Agricola Medal, according to the organization, for his vision, leadership and commitment to food security and nutrition as well as the pursuit of innovative solutions in wheat self-sufficiency in the context of fast-changing and challenging circumstances.

The Prime Minister received the Agricola Medal in the presence of high-level delegates of various countries, representatives of international organizations, diplomatic missions in Italy and private sector representatives.
For the past five years, Ethiopia has been making critical investments in the agricultural sector and pursuing wheat self sufficiency endeavors marking significant growth across major commodities.