የሰላምና አንድነት ማህበር የዋሺንግተን ዲሲ ግብረ ሃይል ተወካዮች በወቅታዊ የአገራችን ጉዳዮች ዙሪያ በኤምባሲያችን በመገኘት ውይይት አድርገዋል።
በግብረ ኃይሉ እና አጠቃላይ በዳያስፖራው ማህበረሰብ የሚነሱ ከሰላምና ጸጥታ፣ ከህገ-መንግስት እና ሌሎች ጉዳዮችን አስመልክቶ ጥያቄያቸውን በደብዳቤ ለክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለ ሰጥተዋል። አምባሳደር ስለሺ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት በአገራቸን ለውጥ እንዲመጣ ብሎም ሲደረጉብን የነበሩ ኢ-ፍትሃዊና ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ተጽእኖዎች በመቃዎም ግብረ ኃይሉ ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።በቃል እና በደብዳቤ የቀረቡ ጥያቄዎችን ለሚመለከተው የመንግስት አካል እንዲደርስ እንደሚያደርጉም ቃል […]
