ክቡር አምባሳደር ስለሺ በቀለ ከበድር ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የሙስሊም ድርጅት ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም የበድር ኢትዮጵያ ተወካዮች በቅርቡ ከእስልምና እምነት ተቋማት እና ከመኖሪያ ቤቶች ጋር በተገናኘ በተለይ በአዲስ አበባ ዙሪያ ተከስተዋል ያሏቸውን ችግሮች አንስተዋል።በድር ኢትዮጵያ ህገ-ወጥነተን እንደማይደግፍ፤ ይሁንና የሚወሰዱ እርምጃዎች ህዝቡን አደጋ ላይ በማይጥል፣ በውይይት እና ወደ ቅሬታ በማያስገባ መልኩ እንዲሆን ጠይቀዋል። ድርጅቱ በቀጣይም አባላቱን በማስተባባር ለአገር ልማት፣ ሰላምና መልሶ ግንባታ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክርም ተናግረዋል። ክቡር አምባሳደር ስለሺ […]